Fana: At a Speed of Life!

በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ የሚታወቁ የአፍሪካ የቀድሞ መሪዎች ልጆች የሕዳሴ ግድብን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ የሚታወቁ የአፍሪካ የቀድሞ መሪዎች ልጆች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ የፓትሪስ ሉሙምባ ልጅ፣ የኒልሰን ማንዴላ የልጅ ልጅ፣ የኳሜ ኑኩሩማ ልጅ፣ የጁልየስ ኔሬሬ ልጅ፣ የኬኔት ካውንዳ ልጅ እና ሌሎችም የአፍሪካ ሕብረት መስራችና የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ጅማሮ ተሳታፊዎች ቤተሰቦች ተሳትፈዋል።

ጎብኚዎቹ ለአፍሪካ ሰላምና ልማት በፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ የሚታወቁ ሲሆኑ÷ በምልከታቸው ኢትዮጵያ በራስ አቅም ይህንን መስራቷ የፈጠረባቸውን መደነቅ አጋርተዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በአካል ተገኝተው ሲመለከቱት ከጠበቁት በላይ ሆኖ እንዳገኙትም ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት ላይ ለመታደም ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ጎብኚዎቹ÷ ወደ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ የተለያዩ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

በመዲናዋ በነበራቸው ጉብኝት ወቅትም ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መስፋፋት የነበራትን ሚና እና ያልተቋረጠ ተጋድሎ የሚያሳዩ ስራዎችን ተመልክተዋል።

በአሸናፊ ሽብሩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.