Fana: At a Speed of Life!

የአምራች ኢዱስትሪዎችን ተግዳሮቶች ለመፍታት …

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአምራች ኢንዱስትሪ ብሔራዊ ካውንስል በደብረሃን ከተማ አምራች ኢዱስትሪዎች የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ ጉብኝት እያካሄደ ነው።

ጉብኝቱ በአምራች ኢንዱስትሪ ብሔራዊ ካውንስል ሰብሳቢ አምባሳደር ግርማ ብሩ የተመራ ሲሆን፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ እና የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ተሳትፈዋል።

እንዲሁም የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በጉብኝቱ ላይ ተገኝተዋል።

የጉብኝቱ ዋና ዓላማ አምራች ኢዱስትሪዎች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ መመልከትና እያጋጠሟቸው ያሉ ተግዳሮቶችን በቅንጅት ለመፍታት የሚያስችል መፍትሄ ለመስጠት እንደሆነ ተገልጿል።

የጀር አግሮ ኢንዱስትሪ፣ ፌቢላ መኪና መገጣጠሚያ፣ ብሮውን ፉድስ፣ ዴዴ ጠርሙስ፣ ጁኒፐር ግላስ በአምራች ኢንዱስትሪ እየተጎበኙ ያሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ናቸው።

አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ያሉበትን የምርት ሂደትና እያጋጠሟቸው ያሉ ተግዳሮቶችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ብሔራዊ ካውንስሉ አቅርበዋል።

በዓለምሰገድ አሳዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.