አልጄሪያ እና ቡርኪና ፋሶ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ አልጄሪያ እና ቡርኪና ፋሶ አሸንፈዋል።
በምድብ አምስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ በአልጀሪያ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3 ለ 1 አሸንፋለች።
የአልጀኢሪያን የማሸነፊያ ግቦች ኢብራሂም ማዛ፣ ፋሬስ ቻይቢ እና ዚነዲን ቤላይድ ሲያስቆጥሩ ኤሚሊዮ ንሱ የኢኳቶሪያል ጊኒን ብቸኛ ግብ ከመረብ አገናኝቷል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ቡርኪና ፋሶ ሱዳንን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችላለች።
በጨዋታው ላሲና ትራኦሬ እና አርሴን ኩዋሲ የቡርኪናፋሶን ግቦች አስቆጥረዋል።
ምድቡን አልጄሪያ ዘጠኝ ነጥብ በመያዝ ስታጠናቅቅ ቡርኪና ፋሶ በስድስት ነጥብ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ የምድብ ስድስት ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ ጋቦን ከኮትዲቯር እንዲሁም ሞዛምቢክ ከካሜሩን ይጫወታሉ።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!