ሀዋሳ ከተማ አዳማ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል።
አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን ግቦች ሽመልስ በቀለ እና ተባረክ ሄፋሞ ከመረብ አገናኝተዋል።
ቀደም ብለው በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች ሀዲያ ሆሳዕና እና መቻል 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ÷ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሲዳማ ቡና እንዲሁም ሸገር ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።