Fana: At a Speed of Life!

የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 130ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) የበዓሉን አከባበር አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ÷ ዳግማዊ ዓድዋን የሚገልጹ በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት ዓመት ላይ መገኘታችን 130ኛውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

በዓሉ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር የገለጹት ሚኒስትሯ÷ ዓድዋ ከኢትዮጵያውያን ባሻገር የመላው ጥቁር ሕዝቦች ድል በመሆኑ ይህንን የሚገልጹ ዝግጅቶች እንደሚኖሩ ተናግረዋል።

በበዓሉ ተሞክሮዎችን ማጋራት የሚያስችሉ እና የሰራዊቱን ጉዞ የሚያሳዩ የተለያዩ ዝግጅቶች በዐውደ ርዕይ እንደሚቀርቡ አንስተው÷ በክብረ በዓሉ የተለያዩ ሀገራት የጦር መሪዎችና ሚኒስትሮች እንደሚታደሙ አመልክተዋል።

በአሸናፊ ሽብሩ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.