Fana: At a Speed of Life!

የአሜሪካ ነዳጅ ጫኝ የጦር አውሮፕላን በኢራቅ ተከሰከሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ነዳጅ ጫኝ የጦር አውሮፕላን በምዕራባዊ ኢራቅ መከስከሱ ተሰምቷል፡፡

የአሜሪካ ጦር ዲፓርትመንት እየበረሩ ላሉ ተዋጊ ጀቶች አየር ላይ ነዳጅ የሚሞላው “ኬሲ-135” አውሮፕላን መውደቁን በማረጋገጥ÷ አደጋው የተከሰተው በጠላት ወይም በወዳጅ ሀገር ተኩስ አይደለም ብሏል።

አደጋው ሁለት አውሮፕላኖች ላይ መከሰቱን ጠቅሶ÷ ነዳጅ መሙያ አውሮፕላኑ ሲከሰከስ ሌላኛው በሰላም መሬት ላይ ማረፉን ገልጿል፡፡

አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ምዕራባዊ ኢራቅ ውስጥ የነፍስ አድን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አመልክቷል።

አውሮፕላኑ ሲወቅድ በሰዎች ላይ ጉዳት ስለመድረሱ የተባለ ነገር የለም።

በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ አምስት የአሜሪካ ወታደሮች በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙም የታወቀ ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ ዘግቧል።

የተከሰከሰው አውሮፕላን በጦርነቶች ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለውና ተዋጊ ጀቶች እና ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች ረጅም ርቀት ተጉዘው ዒላማዎችን በሚመቱበት ወቅት በቂ ነዳጅ እንዲኖራቸው እንደሚያደርግ ተገልጿል።

በሚኪያስ አየለ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.