Fana: At a Speed of Life!

በኒው ዮርክ በተከሰተ የአውሮፕላን አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ ኒዮርክ ከተማ ላጋርዲያ አውሮፕላን ማረፊያ በተከሰተ የአውሮፕላን አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በርካታ ሰዎች መጎዳታቸው ተሰምቷል፡፡

የከተማዋን ፖሊስ ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው÷ ባለቤትነቱ የኤር ካናዳና ሲአርጄ 900 የሚል ሞዴል ያለው አውሮፕላን ከሞንትሪያል ተነስቶ ላጋርዲያ አውሮፕላን ማረፊያ እያረፈ በነበረበት ወቅት ከተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ አደጋ አጋጥሞታል፡፡

በአውሮፕላኑ 76 ሰዎች ተሳፍረው የነበረ ሲሆን÷ በአደጋው ዋናና ረዳት አብራሪዎች ሕይወት ሲያልፍ በርካታ ሰዎች መጎዳታቸው ተመላክቷል፡፡

የአደጋው ምክንያት እስከሚጣራና የተፈጠረው ችግር እስከሚስተካከል አየር መንገዱ በጊዜያዊነት የተዘጋ ሲሆን÷ በረራዎችም መቋረጣቸውን ዘገባው አመላክቷል፡፡

በሚኪያስ አየለ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.