Fana: At a Speed of Life!

ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሀድያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግብ ሄኖክ አርፍጮ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ከ12 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን እያደረጉ ናቸው።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.