በምስራቅ አፍሪካ በሚሊየን የሚቆጠሩ ስደተኞች ለረሀብና ለተመጣጠነ ምግብ እጥረትሊጋለጡ ይችላሉ-ተመድ
አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 21 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በምስራቅ አፍሪካ በሚሊየን የሚቆጠሩ ስደተኞች ለከባድ ረሀብ እና ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሊጋለጡ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ።
የዓለም የምግብ ድርጅት እንደገለጸው ÷ በድርጅቱ በሚሰጡት የምግብ ድጋፍ ላይ ጥገኛ የሆኑ በሚሊየን የሚቆጠሩ ስደተኞች ለባድ ረሀብ እና የተመጣጠነ ምግብ እጦትይጋለጣሉ ብሏል።
ለዚህም ምክንያቱ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ ከለጋሽ አካላት አስፈላጊውን የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት አለመቻሉ መሆኑን አስታውቋል።
ስለሆነም ድርጅቱ በኢትዮጵያ ፣ በኡጋንዳ ፣ በኬንያ ፣ በደቡብ ሱዳን እና በጅቡቲ ስደተኞች ካምፕ ውስጥ ለሚገኙ ከ 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ለሚበልጡ ስደተኞች የሚያደርገውን የምግብ እና የገንዘብ ድጋፉ 30% ያህል ቅናሽ ማድረጉን ገልጿል።
ከዚያም ባለፈ ስደተኞቹ ካምፑ ውስጥ ባለው በቂ ያልሆነ መጠለያ፣ደካማ የጤና አገልግሎት ስርዓት እና በንጹህ የመጠጥ ውሃ ችግር ምክንያት ለኮቪድ -19 መስፋፋት ተጋላጭ ናቸው ብሏል።
ምንጭ፡-ቢቢሲ
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።