Fana: At a Speed of Life!

የዓለም የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) “ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሃን ይመልሳል” በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን እየተከበረ ነው።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ሚኒስቴሩ ከበጎ ፈቃደኝነት ጋር በተያያዘ ሰፋፊ ስራዎች ሰርቷል።

በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ60 በላይ ደም ባንኮች መቋቋማቸውን አንስተው÷ የደም ልገሳ አሁን ላይ ባህል እየሆነ መጥቷል ብለዋል።

ደም የመለገስ ተግባር አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ደም እና ሕብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው÷ በበጀት ዓመቱ ከ441 ሺህ ዩኒት በላይ ደም መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል።

ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር የ19 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸው÷ በበጀት ዓመቱ 338 የዓይን ብሌን ለማሰባሰብ ታቅዶ ከ411 በላይ ማሰባሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።

የሰኔ ወር እስከሚጠናቀቅ ድረስ የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን በተለያዩ መርሐ ግብሮች እንደሚታሰብ ተመላክቷል።

በቅድስት ብርሃኑ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.