Fana: At a Speed of Life!

35 ‘A+’ በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ የተሸለመው የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 35 ‘A+’ በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸልሟል፡፡

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 679 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ከዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች መካከል የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 3 ነጥብ 99 ውጤት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል።

ከ49 ኮርሶች 35 ‘A+’ እና 13 ‘A’ እንዲሁም 1 ‘A-‘ በማምጣት ነው የዩኒቨርሲቲው 8ኛ ዙር ምረቃ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ የሆነው።

ተማሪ አንቲ ምትኩ በቀጣይም በተማረበት ሙያ ለሀገሩ የራሱን አሻራ ለማኖር እንደሚሰራ ተናግሯል፡፡

በዩሱፍ ጁሃር

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.