Fana: At a Speed of Life!

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ይልማ መርዳሳ የምዕራብ አየር ምድብን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ይልማ መርዳሳ የምዕራብ አየር ምድብን ጎበኙ፡፡

በጉብኝታቸው ወቅትም የምድቡ ሰራዊት ከሀዲው ያሴረውን ሀገርን የማተራመስ እቅድ ለማክሸፍ አመራሩ በጥበብ አባላቱም በጀግንነት ውሎ ለፈፀሙት አኩሪ ገድል በማመስገን ጀግኖች ናችሁ ብለዋል።

የምዕራብ አየር ምድብ የሕወሓት ጁንታ ሴራን ለማክሸፍ በተደረገው የህግ ማስከበር ዘመቻ ታላቅ ተጋድሎ እንደፈጸመ ማረጋገጣቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የሀገር መከታ በሆነው የመከላከያ ሠራዊት ላይ ሰው በላው ቡድን የራሱን ጓድ ከኋላው ሆኖ በመውጋቱ አባላቱ የገጠማቸውን ልብ የሚሰብር ሀዘን ችለው የምድቡ አመራርና አባላት ቅንጅት በመፍጠር በሀገራዊ ሞራልና ስሜት የሕዝብ ልጅ መሆናቸውን በተግባር ማስመስከራቸውንም ጠቅሰዋል፡፡

በቀጣይም የቴክኖሎጂ አቅም እና ክህሎትን በማሳደግና የሰው ሀይልን በስልጠና በማብቃት፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አስተሳሰብ ፍፁም ነፃ በመሆን የሪፎርም አደረጃጀቱን ይበልጥ በማጠናከር የሀገር መከታነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.