Fana: At a Speed of Life!

በጉጂ ዞን ኦዶ ሻኪሶ ወረዳ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወደመ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በጉጂ ዞን ኦዶ ሻኪሶ ወረዳ በማገዶ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወደመ።

በትናትናው ዕለት በከተማዋ በደረሰ የእሳት አደጋ 29 መኖሪያ ቤቶች እና የንግድ ቤት መውደማቸው ተጠቁማል።

የወረዳው መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ በዳሶ ታደሰ የእሳት አደጋው በኤሌክትሪክ ሀይል ምክንያት ሳይከሰት እንደማይቀር ገልፀዋል።

በአደጋው የ19 አባወራዎች ንብረት ሙሉ በሙሉ መውደሙን ሃላፈው ተናግረዋል።

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- ወረዳhttps://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.