በምርጫው የተወዳደሩ ግለሰቦች ልምዳቸውን እያካፈሉ ነው
የፖለቲካ ፓርቲ እጩዋ ፀጋነሽ ጋማቶ በበኩላቸው÷ ምርጫው ኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የገለጠችበት ነው ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ማጭበርበርና መቶ በመቶ አሸንፈናል የሚባልበት እንደነበር አንስተው÷ አሁን ግን ነፃ ተቋም በማቋቋም የተካሄደ ነው ብለዋል።
የግል ተወዳዳሪው አቶ ገላሳ ዲልቦ አስቀድመው በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ኢትዮጵያ ስላገኘችው ዲፕሎማሲያዊ ድል እንኳን ደስ አለን ብለዋል።
ምርጫውና የግድቡ ሂደት ለኢትዮጵያዊያን ተስፋ የሰጠ ብለውታል።
ምርጫውም ከስርቆትና ውዝግብ ተላቆ በአዲስ ምዕራፍ የተካሄደ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ምርጫው ለኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ሥርአት መሰረት የጣለ እንደሆነም አክለዋል።

