Fana: At a Speed of Life!

አገር የማዳን ጉዳይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ ሳይሆን የእኔም ነው – ድምፃዊ አቡሽ ዘለቀ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አገር የማዳን ጉዳይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ አይደለም ሲል ድምፃዊ አቡሽ ዘለቀ ተናገረ፡፡

ድምፃዊ አቡሽ ዘለቀ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበረዉ ቆይታ ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ወደ ግምባር መዝመታቸውን አስታውሶ ÷ አገር የማዳን ጉዳይ ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ አይደለም ብሏል፡፡

በዚህ ወቅት ሀገራችን በምትፈልገን ዘርፍ ሁላችንም ተሰላፊ መሆን አለብን ያለው ድምፃዊ አቡሽ ፥ ኢትዮጵያን ከአባቶቻችን የተረክብናት አገር ናት ፤ እኛ ደግሞ ለልጆቻችን ጠብቀን የማቆየት ሀላፊነት አለብን ነው ያለዉ፡፡

ለልጆቻችን የምናወርሳትን አገር ደግሞ ህልዉናዋ አደጋ ውስጥ በወደቀበት ወቅት ልንታደጋት ይገባል ብሏል፡፡

ሌላ አገር የለንም ፥ ያለችን አንድ አገር ናት፥ ያለችን አንድ አገር እንድትፍርስ አንፈቅድም ብሏል፡፡

እንደ ግለሰብ አገሬ ከእኔ የምትጠብቀውን ነገር ለማድረግ ዝግጁ ነኝ ፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ም ዝግጁ ሊሆን እንደሚገባም ድምፃዊ አቡሽ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.