ስፓርት
የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን ከ16 አመት በኋላ ተሰበረ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን ትናንት ማታ በዑጋንዳዊው አትሌት ቼፕቴጌ ተሻሽሏል፡፡
ጆሹዋ ቼፕቴጌ ትናንት ምሽት በሞናኮ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር የ5 ሺህ ሜትሩን ክብረ ወሰን በሁለት ሰከንዶች አሻሽሎታል፡፡
አትሌቱ ርቀቱን 12 ደቂቃ ከ35 ሰከንድ ከ36 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ ነው ክብረ ወሰኑን ማሻሻል የቻለው፡፡
የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን በኢትዮጵያዊው ቀነኒሳ በቀለ ላለፉት 16 አመታት ተይዞ የቆየ ነበር፡፡
Read More...
በቻምፒየንስ ሊጉ ሙኒክ ባርሴሎናን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸንፎታል
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት ምሽት በተደረገ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ባርሴሎና ከባድ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
በሊዝበን በተደረገው ጨዋታ የጀርመኑ ባየርን ሙኒክ ባርሴሎናን 8 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፎታል፡፡
በጨዋታው ቶማስ ሙለር እና ተቀይሮ የገባው ፊሊፔ ኮቲንሆ ለሙኒክ ሁለት ሁለት ጎሎችን አስቆጥረዋል፡፡
ቀሪዎቹን…
ዊሊያን በሶስት አመታት ውል አርሰናልን ተቀላቀለ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ብራዚላዊው የመስመር አማካር ዊሊያን የሰሜን ለንደኑን የእግር ኳስ ክለብ አርሰናልን ተቀላቀለ፡፡
ዊሊያን የምዕራብ ለንደኑን እግር ኳስ ክለብ ቼልሲን በመልቀቅ ወደ አርሰናል በነጻ ዝውውር አምርቷል፡፡
የ32 አመቱ ዊሊያን በአርሰናል ለሶስት አመታት ለመቆየት መስማማቱም ነው የተነገረው፡፡
ዊሊያን በፈረንጆቹ 2013…
በቻምፒየንስ ሊጉ አር ቢ ሌፕዚግ የግማሽ ፍጻሜተፋላሚ መሆኑን አረጋገጠ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት ምሽት የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ተካሄዷል፡፡
አር ቢ ሌፕዚግ እና አትሌቲኮ ማድሪድን ባገናኘው ጨዋታ የጀርመኑ ክለብ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
በፖርቹጋል ሊዝበን በተደረገው በዚህ ጨዋታ አር ቢ ሌፕዚግ ጨዋታውን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ኦልሞ እና አዳምስ ለአርቢ…
በዩሮፓ ሊግ ሲቪያ እና ሻካታር ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተካሄደዋል፡፡
በጀርመን እየተደረገ ባለው ውድድር የስፔኑ ሲቪያ እና የዩክሬኑ ሻካታር ዶኔስክ ግማሽ ፍጻሜ መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ከእንግሊዙ ወልቨርሃምፕተን ወንደረርስ ጋር የተጫወተው ሲቪያ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በጨዋታው ወልቭሶች አዳማ ትራኦሬ…
በዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚዎች ተለይተዋል
አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚዎች ተለይተዋል፡፡
ከትናንት በስቲያ እና ትናንት በተደረጉ የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች በሩብ ፍጻሜ የሚጫወቱ 8 ቡድኖች ታውቀዋል፡፡
የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎቹ የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ የሚደረጉ ይሆናል፡፡
ሰኞ ማንቼስተር ዩናይትድ ከዴንማርኩ ኮፐንሃገን እንዲሁም የጣሊያኑ ኢንተርሚላን…