Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል ከ186 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ186 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የኦሮሚያ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታውቋል፡፡

የቢሮው ኃላፊ አቶ አህመድ ኢድሪስ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ÷ ከ 186 ቢሊየን ብር ካፒታል በላይ ላስመዘገቡ 3 ሺህ 600 በላይ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቷል ብለዋል፡፡

ፍቃድ ከተሰጣቸው መካከልም 92 የኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ጥያቄ ያቀረቡ ፣ 1 ሺህ 502 ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ፣ 47 ዩኒየኖች እንዲሁም 1 ሺህ 680 የሀገር ውስጥና የዳስያስፖራ ባለሃብቶች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል፡፡

ባለሃብቶቹ በሙሉ አቅማቸው ወደስራ ሲገቡ ከ679 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩም አቶ አህመድ መናገራቸውን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.