Fana: At a Speed of Life!

የአርቲስት ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈፀመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጣሊያን ሮም ከተማ በድንገት ሕይወቱ ያለፈው የክላርኔት የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋቹ የአርቲስት ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈፀመ።

በሀገር ፍቅር ቲዓትር ቤት የሙያ አጋሮቹ  የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ከተከናወነ በኋላ በመንበረ ፀባኦት ቅድስ ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ተፈፅሟል፡፡

በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አርቲስቶች፣ የአርቲስቱ ወዳጆች እና ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

በምንተስኖት ሙሉጌታ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.