Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሐላላ ኬላ ሪዞርትን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሐላላ ኬላ ሪዞርትን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በይፋ ተረክቧል፡፡

የክልሉ መንግስት የ’ገበታ ለ ሀገር’ ፕሮጄክት አካል የሆነው እና በኮይሻ ፕሮጄክት ክላስተር ሥር የለማውን የሐላላ ኬላ ሪዞርት ነው ከጽህፈት ቤቱ የተረከበው፡፡

ሪዞርቱን ‘ሐላላ ኬላ ሪዞርት’ በሚል ስያሜ ለማስተዳደር የክልሉ መንግሥት ከፓራዳይዝ ሎጅዎች፤ ሪዞርቶች እና ሆቴሎች ማኔጅመንት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር ስምምነት ማድረጉን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.