በሱዳን የሚገኙ ዜጎችን ደኅንነት ለመጠበቅ እየተሠራ ነው – አምባሳደር ብርቱካን
መንግስት ዜጎችን ከሱዳን ለማስወጣት ካሳየው ቁርጠኛ አቋምና እየወሰደ ካለው ጠንካራ እርምጃ አኳያ በተከናወኑ ስራዎች የተገኙ መልካም ውጤቶችንና ያጋጠሙ ፈተናዎችን በግምገማው ላይ ማንሳታቸውን አምባሳደር ብርቱካን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህም በቀጣይ ለምናካሂደው ስምሪት ጠቃሚ ሐሳቦችን ተለዋውጠናል ብለዋል አምባሳደሯ፡፡