Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የ2015 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል የ2015 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በምሥራቅ ሸዋ ዞን ተካሄደ።

ከክልል እስከ ወረዳ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እና ከክልሉ የተወጣጡ ግንባር ቀደም ወጣቶች በመርሐ- ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

በዕለቱም የችግኝ ተካለ፣ የቤት ዕድሳት እና የደም ልገሳ መከናወኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በ2015 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 9 ነጥብ 5 ሚሊየን ወጣቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡

በዚህም ከ23 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ነው የታሰበው፡፡

በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱም 3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገመት አገልግሎትእንደሚሰጥ ነው የተመላከተው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.