በአቶ አህመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ በባህርዳር የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኘ ነው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በገንዘብ ሚስትር አህመድ ሺዴ የተመራ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ በባህርዳር ከተማ እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኘ ነው፡፡
በጉብኝት መርሐ ግብሩ የባህርዳር ከተማ ከንቲባ ድረስ ሳሕሉ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች መሳተፋቸውንም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡