ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበት የመግባቢያ ሥምምነት በመፈረሙ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የደስታ መልዕክት አስተላለፈ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበት የመግባቢያ ሥምምነት በመፈረሙ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የደስታ መልዕክት አስተላለፈ።
የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች የስምምነት ሠነዱ መፈረሙን አስመልክቶ የደስታ መግለጫ ስነ-ስርዓት አካሂደዋል።
በስነ-ስርዓቱም የኢፌድሪ መንግስት እና የሶማሌላንድ መንግስት የፈረሙት የትብብር እና የአጋርነት መግባቢያ ሠነድን በተመለከት የ’እንኳን ደስ ያለን’ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።