ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከተመድ የንግድና ልማት ኮንፍረንስ ያላደጉ ሀገራት ልዩ ፕሮግራም የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የንግድና ልማት ኮንፍረንስ ያላደጉ ሀገራት ልዩ ፕሮግራም የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር ከሆኑት ፓውል አኪዊሚን ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም÷ በዋናነት የተባበሩት መንግስታት የንግድና ልማት ኮንፍረንስ በኢትዮጵያ በሚሰራቸው የልማትና ሌሎች የትብብር ስራዎች ዙሪያ መክረዋል።