Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኘው የፓቶሎጂ ሙዝየም በአዲስ መልክ ታድሶ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በ1974 ዓ.ም የተቋቋመው የፓቶሎጂ ሙዝየም በአዲስ መልክ እድሳት ተደርጎለት በዛሬው ዕለት ተመረቀ፡፡

የኮሌጁ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዱዓለም ደነቀ (ፕ/ር) በምረቃው ላይ ባደረጉት ንግግር ለበርካታ ዓመታት ለሕክምና ተማሪዎች ማስተማሪያነት ሲያገለግል የነበረው ሙዝየም÷ በቀድሞው የጤና ሚንስትር ዶክተር ከበደ ታደሰ ቤተሰቦች ድጋፍ በአዲስ መልክ ታድሶ መመረቁን አስታውቀዋል፡፡

ሙዝየሙ የጤና ባለሙያዎችን በማስተማር እና በፓቶሎጂ ዘርፍ ምርምሮችን ለማስፋፋት ያለውን ፋይዳ ጠቁመው÷ ለተማሪዎች፣ ተመራማሪዎች እና የጤና እንክብካቤ ባለሙያዎች ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆን ማስረዳታቸውን የኮሌጁ መረጃ አመላክቷል፡፡

የዶክተር ከበደ ባለቤት ወ/ሮ እመቤት ደጀኔ በበኩላቸው÷ የባለቤታቸውን የዶክተር ከበደ ታደሰ ራዕይ እውን ለማድረግ ቤተሰባቸው የፓቶሎጂ ሙዝየሙን በአዲስ መልክ ማዘጋጀቱን በመግለጽ ፕሮጀክቱ እንዲሳካ ላደረጉት ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ለጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና ለፓቶሎጂ ትምህርት ክፍል ምስጋና አቅርበዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.