Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በ183 ጣቢያዎች ፈተናው መሰጠት መጀመሩን የቢሮው ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች የፈተና አስፈጻሚዎችን ጨምሮ በቂ የጸጥታ አካላት መመደባቸውንም አስታውቀዋል።

ተማሪዎች ለፈተናው ብቁ እንዲሆኑ የማጠናከሪያ ትምህርትን ጨምሮ ደረጃቸውን የሚመጥን ሞዴል ፈተና መሰጠቱን አስታውሰዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.