Fana: At a Speed of Life!

ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ከኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ካቢኔ ፀሃፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ከኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ካቢኔ ፀሃፊ ኪፕቹምባ ሞርኮሜን ጋር በኬንያ ተወያተዋል፡፡

በውይይታቸውም ሁለቱን ሀገራት በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር በሚቻልባቸው ጉዳዮች መክረዋል።

በተጨማሪም የንግድ፣ የኢኮኖሚ ዕድገት እና የጋራ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ማድረጋቸውን ከኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በውይይቱ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ መሳተፋቸው ተገልጿል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.