Fana: At a Speed of Life!

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በምህንድስና፣ በጤና እና በሃብት አሥተዳደር ዘርፍ ትምህርታቸውን በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም በምህንድስና የትምህርት ዘርፍ በዶክትሬት ዲግሪ መከታተላቸው ተገልጿል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ፍጹም አሰፋን (ዶ/ር) ጨምሮ የመከላከያ ሚኒስትር ዴዔታዎች፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖችና የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል።

በሦስት ኮሌጆች እና በአንድ የምርምር እና ልማት ኢንስቲትዩት የተዋቀረው ዩኒቨርሲወቲው÷ በመጪዎቹ ዓመታት በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች ቀዳሚ የመሆን ራዕይ አንግቦ እየሠራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ከኢትዮጵያ ተማሪዎች በተጨማሪ ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ተማሪዎችንም አሰልጥኖ እያስመረቀ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.