Fana: At a Speed of Life!

ከዱር እንስሳት አጠቃቀም ከ62 ሚሊየን ብር በላይ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ሥድስት ወራት 74 ሺህ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች በኢትዮጵያ የሚገኙ ብሔራዊ ፓርኮችን ጎብኝተዋል፡፡

በግማሽ ዓመቱ በአጠቃላይ ከእንስሳት አጠቃቀም ከ62 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ለፋና ዲጂታል አስታውቋል፡፡

ከተገኘው ገቢ 49 ነጥብ 8 ሚሊየን ያህሉ ከዱር እንስሳት ፍጆታዊ አጠቃቀም (ሕጋዊ አደን) መሆኑንም አስረድቷል፡፡

ከኢ-ፍጆታዊ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ደግሞ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር መገኘቱን ነው ያስታወቀው፡፡

የተሻለ የጎብኝ ቁጥር ካስተናገዱት ብሔራዊ ፓርኮች መካከል÷ ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ አብጃታ ሻላ ሐይቆች ብሔራዊ ፓርክ እና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተጠቅሷል፡፡

በኢትዮጵያ 27 ብሔራዊ ፓርኮች እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

በዮሐንስ ደርበው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.