Fana: At a Speed of Life!

ደረጃ የወጣላቸው ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም አለባቸው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው ሁሉም ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አሳሰበ፡፡

የኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ሀብቴ÷ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅትና ለብሌስ አግሮ ፉድ ኢንዱስትሪ ውክልና በመስጠት ብሔራዊ የደረጃ ምልክት ሲሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል ።

አሁን ላይ ግን ኢንስቲትዩቱ ውክልናውን በማንሳት ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ አስገዳጅ ደረጃ ለወጣላቸው ምርቶች ብሄራዊ የደረጃ ምልክት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።

በሀገሪቱ ለ370 ምርቶች አስገዳጅ ደረጃ መውጣቱን ጠቁመው÷እነዚህ ምርቶች ብሄራዊ የደረጃ ምልክት ካልተጠቀሙ ርምጃ እንደሚወሰድባቸው አሳስበዋል ።

ብሄራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም የተጠቃሚዎችን ጤንነት ለመጠበቅና የምርት ባለቤቶች በተመሳሳይ ምርት ጉዳት እንዳይደርስባቸው እንደሚያስችልም አስገንዝበዋል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.