ባሕርዳር ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባሕርዳር ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል።
የጣና ሞገዶቹን የማሸነፊያ ግቦች ግርማ ዲሳሳ እና ቸርነት ጉግሳ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ቀጥሎ በተካሄደው የሊጉ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና መቻል 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።