Fana: At a Speed of Life!

አሌክሳንደር አርኖልድ ከልጅነት ክለቡ ጋር እንደሚለያይ አረጋግጧል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከልጅነት ክለቡ ሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

አሌክሳንደር አርኖልድ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ራሱን በአዲስ ክለብ እና በተለየ ቦታ ለመፈተሽ በመፈለጉ ከሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

ወደ አዲስ ክለብ መሄዱም ያለውን ሙሉ አቅም አውጥቶ እንዲጠቀም እንደሚያስችለው ነው የገለጸው፡፡

ላሳደገው ክለብም ያለውን ክብር እና ፍቅር ገልጾ፤ ለመልቀቅ የወሰነው ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ጉዳይ አለመሆኑን ጠቅሷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.