Fana: At a Speed of Life!

ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የእምነት ተቋማት ሚና እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የእምነት ተቋማት ያላቸውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ አስገነዘቡ፡፡

3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

ፕሬዚዳንት ታዬ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የሃይማኖት መሪዎች ለሀገር የሰላም ግንባታ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የሃይማኖት አባቶች ያላቸውን የማይተካ ሚና የበለጠ ማጉላት እንደሚገባቸውም በአጽንኦት መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

እርስበርስ መረዳዳትና መደጋገፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በቀላሉ ለመወጣትና ሰላምና ልማትን ለማስቀጠል ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የጀመረችው ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን የሃይማኖት አባቶች ሚና የጎላ መሆኑንም አስረድተው፤ ሚናቸውን የበለጠ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.