Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የኢንዱስትሪ መንደር…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ መንደር ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ፡፡

ከንቲባ አዳነች በአዲስ አበባ ከተማ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ መንደር ጎብኝተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም የነዋሪዎችን ጥያቄ የምንመልሰው የሚታዩ ፣ የሚጨበጡ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ በማተኮር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

93 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የኢንዱስትሪ መንደሩ የመጀመሪያው ምዕራፍ ከ120 በላይ ሼዶች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡

ሼዶቹ ለብረታብረት ሥራ፣ ለእንጨት ውጤቶች፣ ለጨርቃ ጨርቅ፣ ለፕላስቲክ እና ለኬሚካል ማምረቻነት፣ የምርት ማሳያ እና መሸጫ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ናቸው።

የኢንዱስትሪ መንደሩ ግንባታ የመስሪያ ቦታ ችግርን ከማቃለል ባሻገር የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያስችላል ነው ያሉት፡፡

በተጨማሪም ሰፊ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና የኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥ ረገድ ሚናው ጉልህ ነው ያሉት ከንቲባዋ÷ የግንባታው 2ኛ ምዕራፍ ለአግሮ ፕሮሰሲንግ ምርቶች የሚሆኑ ሼዶችን የያዘ ነው ብለዋል።

የኢንዱስትሪ መንደሩ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ሼዶች በተለየ ሁኔታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግብዓቶችን እንዲጠቀም ተደርጎ እየተገነባ ነው።

ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በጥቂት ደቂቃ መድረስ የሚያስችል አዲሱ የአቃቂ ቦሌ ካርጎ መንገድ ላይ እና ምርት ማጓጓዝን ታሳቢ ያደረገና ስትራቴጂክ ስፍራ ላይ እንደሚገኝም የከንቲባ ጽ/ቤት ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.