የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለሁሉም አረዓያ የሚሆን ነው – የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ለሁሉም ሀገራት አረዓያ የሚሆን ነው አሉ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ውጥን እንዲሳካ በማድረግ ረገድ የዘመናዊ አመራር ተምሳሌት መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም ኢትዮጵያ የአየር ንብረትን ለውጥ ለመከላከል ትልቅ አስተዋጽኦ በሚያበረክተው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እያስመዘገበች ያለውን ለውጥ አድንቀዋል፡፡
የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ አደጋ የደቀነ እና ተግባራዊ እርምጃ የሚያስፈልገው የጋራ ጉዳያችን ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ ለችግሩ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት አብነት የሚሆን ስራ ማከናወኗን ገልጸዋል።
ይህም የኢትዮጵያን ራዕይና ቁርጠኝነት ያሳያል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
በአፍሪካ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር የያዙ ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የጋራ ህልም ይዘው ለአፍሪካ የተሻለ እጣ ፋንታ መስራት እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
ከሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል 70 በመቶ የሚሆኑት እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች መሆኑ ደግሞ ትልቅ እድል መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ውጥን እንዲሳካ በማድረግ ረገድ የዘመናዊ አመራር ተምሳሌት መሆናቸውንም አንስተዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!