የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 48ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር ጋር ለሁለተኛው ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የእድገት ልማት ፖሊሲ ማስፈፀሚያ የሚውል 258,100,000 ኤስ.ዲ.አር እና ለፍጥነት መንገድ ልማት ድጋፍ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል 27,300,000.00 ኤስ.ዲ.አር የፋይናንስ ድጋፍ እና የብድር ስምምነቶችን ለማጽደቅ በቀረቡ ሁለት ረቂቅ አዋጆች ላይ ነው፡፡