Fana: At a Speed of Life!

ሲዳማ ክልል 13 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲዳማ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት 13 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ፡፡

በቢሮው የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና አሳባሰብ ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ሙላት ዮሴፍ እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ ከሁሉም አማራጮች የሚገኘውን ገቢ በሚገባ ለመጠቀም በትኩረት ተሰርቷል፡፡

ከመደበኛ ግብር ከፋዮችና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 15 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱንም አስረድተዋል፡፡

የገቢ አሰባሰብ ሒደቱን ለማሳለጥ ለባለሙዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ አዳዲስ አሰራሮች መተግበራቸውን ነው ያብራሩት፡፡

በዚህም በበጀት ዓመቱ 13 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የአቅዱን 89 በመቶ ማሳካት መቻሉን ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በክልሉ 45 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች መኖራቸውን የጠቀሱት ወ/ሮ ሙላት÷ በወቅቱና በታማኝነት እንዲከፍሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተከናውኗል ብለዋል፡፡

ከብልሹ አሰራርና ከግብር ሥወራ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ ርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝም አመልክተዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.