Fana: At a Speed of Life!

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለማዕድን ዘርፉ ዕድገት እንደ ማስፈንጠሪያ…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው ለማዕድን ዘርፉ ዕድገት ማስፈንጠሪያ ሆኖ አገልግሏል አለ የማዕድን ሚኒስቴር፡፡

የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ (ኢ/ር) እንዳሉት ÷ በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ እና አበረታች ውጤት ተመዝግቧል፡፡

ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ገቢራዊ ያደረገችው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የጎላ አበርክቶ እንዳለው ነው ያስረዱት፡፡

ከወርቅ ምርት የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከማሳደግ ጀምሮ የማዕድን ዘርፉ ዕድገት ማስፈንጠሪያ ሆኖ ማገልገሉን ተናግረዋል፡፡

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን ብቻ ሳይሆን ተኪ ምርቶችን ጭምር በማበረታታት ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዘርፉ ላስመዘገበችው ስኬት ከዘርፉ ተዋንያን ጋር የነበራት ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ሚናው የጎላ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ የድንጋይ ከሰል ከውጭ ለማስመጣት እስከ 300 ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሩ÷ የድንጋይ ከሰል አቅርቦት እጥረት በመከሰቱ ሲሚንቶ ማምረትና ለገበያ ማቅረብ አስቸጋሪ ነበር ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ በ2017 አራት የድንጋይ ማጠቢያ ፋብሪካዎችን በማስመረቅ የሲሚኒቶ ምርትን አቅርቦት ማሳደግና ዋጋውን መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በቅርቡ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የጋዝ ምርት ለገበያ እንደምታቀርብ ጠቁመው÷ የማዕድን ዘርፉ ለኢኮኖሚ ጥቅም እንዲውል እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

እንደ ሀገር ድፍድፍ ዘይትን ጨምሮ ጥቅም ላይ ያልዋሉ የማዕድን ሀብቶች እንዳሉና እነዚህን ሃብቶች ለሀገር ጥቅም ማዋል እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የአፈር ማዳበሪያ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ÷ ሀገራችን ያላትን ሰፊና ለም የእርሻ መሬት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል ይገባል ነው ያሉት፡፡

ለኢትዮጵያ ጋዝ ማውጣት ከሽያጭ ባለፈ በስፋት ጥቅም ላይ የሚውለውን የዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል አቅም መፍጠር እንደሚያስችልመናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.