Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በተሻለ ትጋትና ቁርጠኝነት መስራት ይገባል – አቶ አደም ፋራህ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ሁሉም አመራርና አባላት በተሻለ ትጋት ሊሰሩ ይገባል አሉ በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡

አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የ2017 በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፍ የትጋት እና የስኬት ዓመት ነበር።

መላው የፓርቲ አመራርና አባላት በተባበረ ክንድ ተናበው መትጋት በመቻላቸው በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት።

በ2017 ዓ.ም በተሰሩ ሥራዎች 3 ዋና ዋና ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው÷ እነዚህም የውስጠ ፓርቲ ጥንካሬ መጎልበት፣ የስትራቴጂያዊ ትብብርና አጋርነት መረጋገጥ እንዲሁም የሀገርና የሕዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻል ናቸው ብለዋል፡፡

ህዝብ በልማት ተጠቃሚ እንዲሆን የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩና በሰላምና መረጋጋት ረገድ የተሰሩ ሥራዎችም በሀገር ደረጃ አንጻራዊ ሰላም እንዲሰፍን እንዳስቻሉ መናገራቸውን ፓርቲው ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

2018 በጀት ዓመት ልዩ ዓመት መሆኑን የጠቀሱት አቶ አደም ፥ ሁሉም አመራርና አባላት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ከባለፈው በጀት ዓመት በተሻለ ትጋትና ቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.