Fana: At a Speed of Life!

አየር መንገዱ ወደ ያቤሎ በረራ ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ ሶስት ሳምንታዊ በረራዎችን ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቅቋል።

አየር መንገዱ ነሐሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ስራ ወደሚጀምረው የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ በረራ ለመጀመር መዘጋጀቱን ለፋና ዲጂታል በላከው መረጃ አስታውቋል።

ያቤሎ እና አካባቢው ከፍተኛ የቀንድ ከብት እርባታ የሚካሄድበትና ለእርሻ የሚውል ሰፊ መሬት ያለበት ስፍራ በመሆኑ አውሮፕላን ማረፊያው ለአካባቢው ማህበረሰብ ኢኮኖሚያው እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል።

ከዚህም ባለፈ በአካባቢው ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክር ነው።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.