Fana: At a Speed of Life!

የ12ኛ ክፍል ውጤት እስከ ነገ ይፋ ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እስከ ነገ ድረስ ይፋ ይደረጋል አለ የትምህርት ሚኒስቴር።

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ነው ይህንን የገለጹት።

በዚህም ውጤቱ እስከ ነገ ቀን 6፡00 ድረስ እንደሚለቀቅ ተናግረዋል።

በአጠቃላይ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች በወሰዱት ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኬሚስትሪ የትምህርት ዓይነት ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን እና በአፕቲትዩድ ደግሞ ዝቅተኛው ውጤት መመዝገቡን አብራርተዋል።

ለትምህርት ቤቶች ሲደረግ የነበረው ድጋፍ፣ ለመምህራን የተሰጠው ስልጠና፣ የተማሪዎች እና የወላጆች ጥረት ለውጤቱ መሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷልም ነው ያሉት።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.