Fana: At a Speed of Life!

በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያመጣው ተማሪ… ካሊድ በሽር

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ካሊድ በሽር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 591 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

እንደ ኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ መረጃ ተማሪ ካሊድ በሽር እንግሊዘኛ 96፣ ሒሳብ 100፣ ፊዚክስ 100 ኬሚስትሪ 98፣ ባዮሎጂ 99፣ አፕቲትዩድ 98 አምጥቷል፡፡

የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር ደቱ ዲቦ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ ተማሪ ካሊድ በሽር በትምህርቱ በጣም ጎበዝ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር ያለው እና አርአያ የሆነ ተማሪ ነው፡፡

በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱ መደሰታቸውንም ገልጸዋል፡፡

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተናን ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ 8 ነጥብ 4 በመቶ ተማሪዎች ብቻ ናቸው ከ50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት ያለፉት፡፡

50 ት/ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ያሳለፉ ሲሆን ÷1 ሺህ 249 ት/ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.