Fana: At a Speed of Life!

ድሬዳዋ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል።

ቀን 9:00 ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሲዳማ ቡና እና ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የሲዳማ ቡና ግቦችን ፍቅረየሱስ ተ/ብርሃን እና ብርሃኑ በቀለ ሲያስቆጥሩ፤ የምድረ ገነት ሽረን ግብ አቤል ማሙሽ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ሜዳ ምሽት 12:00 ላይ በተካሄደው የድሬዳዋ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታ 2 ለ 1 ተጠናቅቋል።

የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ያሬድ ታደሰ እና አብዱሰላም የሱፍ ከመረብ ሲያገናኙ፤ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ዳዊት ገብሩ አስቆጥሯል።

ቀን 9:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የኢትዮጵያ መድን እና አርባ ምንጭ ከተማ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.