Fana: At a Speed of Life!

ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከቡና፣ ሰሊጥና ጥራጥሬ ምርት ላኪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር መመለስ ላይ በሚታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ከቡና፣ ሰሊጥ እና ጥራጥሬ ላኪዎች ጋር ተወያይተዋል።

በምክክር መድረኩ ባንኩ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ የመጠበቅ እና የኤክስፖርት ገቢ በወቅቱ እና በግልጸኝነት እንዲመለስ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለበት ተመላክቷል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ከሕጋዊ ርምጃ በፊት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ማድረግን እንደሚያስቀድም ተጠቅሷል፡፡

ባንኩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑም ተገልጿል፡፡

ከዚህ ባለፈም ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሚሰማው የወጪ ንግድ ልምዶችን የማበረታታት እና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱን የማሳደግ ሥራውን እንደሚያጠናክር አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.