Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 9 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ የለማ ሰብል ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ2017/18 ምርት ዘመን በመኸር ከለማው ከ11 ሚሊየን ሔክታር መሬት ውስጥ እስካሁን 9 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ የሰብል ምርት ተሰብስቧል፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አወሉ አብዲ በሰሜን ሸዋ ዘን እየተከናወነ የሚገኘውን የምርት አሰባሰብ ሒደት ተመልክተዋል፡፡

አቶ አወሉ አብዲ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በክልሉ የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

በዘርፉ የተሻሻሉና ዘመናዊ መሳሪያዎችን በመጠቀም በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረውን ጥረት እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል፡፡

በክልሉ በመኸር እርሻ ከ11 ሚሊየን ሔክታር መሬት በላይ በሰብል መሸፈኑን ጠቁመው÷ እስካሁን 9 ሚሊየን ሔክታር መሬት ላይ የደረሱ ሰብሎች መሰብሰባቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ368 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ውስጥ እስካሁን ከ270 ሚሊየን ኩንታል በላይ መሰብሰቡን አስረድተዋል።

በክልሉ የምርት ብክነት እንዳይኖር የደረሱ ሰብሎችን በኮምባይነር የመውቃት እና የመሰብሰብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በዮሐንስ በቀለ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.