Fana: At a Speed of Life!

ሴኔጋል ግብጽን በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሴኔጋል ግብጽን በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፋለች።

ምሽት 2 ሰዓት ላይ በተጀመረው ጨዋታ ሴኔጋል ግብጽን 1 ለ 0 ስትረታ ሳዲዮ ማኔ የማሸነፊያ ግቧን ከመረብ አሳርፏል።

ውጤቱን ተከትሎ ለፍጻሜ ያለፈችው ሴኔጋል ከሞሮኮ እና ናይጀሪያ አሸናፊ ጋር በፍጻሜ ጨዋታው ትገናኛለች።

የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የውድድሩ አስተናጋጅ ሀገር ሞሮኮ እና ናይጄሪያ ይገናኛሉ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.