Fana: At a Speed of Life!

የወጣቶች ስብዕና ማዕከላት በሥነ ምግባርና ክህሎት የታነጸ ዜጋን ለማፍራት…

‌‎አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የወጣቶች ስብዕና ማዕከላት በሥነ ምግባር እና ክህሎት የታነጸ ዜጋን ለማፍራት ጉልህ ሚና አላቸው አሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፡፡
በዘመናዊ መልክ እድሳት የተደረገለትና አዲስ የተገነባ የስፖርት መጫወቻ ሜዳን ያካተተው የአጋሮ ከተማ የወጣቶች ስብዕና ማዕከል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር )በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ለቀጣይ ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ እና ለሀገር ብልጽግና የወጣቶችን ስብዕና እና ክህሎት መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡
ለዚህም ወጣቶች በሥነ ምግባር ታንጸውና ተኮትኩተው የሚያድጉባቸው ማዕከላት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
‎የአጋሮ ከተማ የወጣቶች ስብዕና ማዕከል የመንግሥት፣ የማሕበረሰቡና የአጋር አካላት የተቀናጀ ጥረትና የመደመር ውጤት መሆኑን አንስተዋል።
‎በከተማዋና አካባቢው የሚገኙ ወጣቶች በማዕከሉ በአግባቡ እንዲገለገሉና አስፈላጊውን እንክብካቤ እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል፡፡
‎ወጣቶች በመልካም ስብዕና ታንጸው፣ እውቀትና ክህሎታቸውን በማዳበር ለአካባቢያቸው ብሎም ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
‎ማዕከሉ ዲጂታል ቤተ መጽሐፍት፣ አይ ሲ ቲ፣ የስልጠና አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች፣ ካፍቴሪያና የምክር አገልግሎትን መስጠት የሚያስችሉ ክፍሎችን ያካተተ መሆኑን ሚኒስቴሩ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
‎የአጋሮ ከተማ ከንቲባ አቶ ናዚፍ መሃመድ አሚን በበኩላቸው ÷ በከተማዋ የወጣቶችን ሁለንተናዊ አቅም ለማሳደግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.