Fana: At a Speed of Life!

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የእኩልነት፣ ዝግጁነትና ክራይስስ ማኔጅመንት ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ሕብረት የእኩልነት፣ ዝግጁነት እና ክራይስስ ማኔጅመንት ኮሚሽነር ሀጃ ላህቢብ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት÷ አውሮፓ ሕብረት ከዓለም አቀፍ የጤና እክሎች ጋር በተያያዘ በተለይም በቅርቡ የኢቦላ ወረርሽኝን ለመከላከል ለተደረገው ጥረት ላሳየው አጋርነትና ድጋፍ አመስግነዋል።

ሕብረቱ ለአፍሪካ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል የሰጠው ድጋፍ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ዓለም አቀፍ ስጋቶችን በጋራ ለመከላከል ወሳኝ ርምጃ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ ስላለው ሰላምና ደህንነት ሁኔታ ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።

ኮሚሽነር ሀጃ ላህቢብ በበኩላቸው÷ የአውሮፓ ሕብረት ከአፍሪካ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከርና በጋራ የጤና እና የሰብዓዊ ቀውሶች ዙሪያ በቅንጅት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.