Fana: At a Speed of Life!

በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ 805 ነጥብ 3 ሚሊየን ችግኞች ተተክለዋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዘንድሮው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር 805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ÷ በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሀገር አቀፍ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሐ ግብር 26 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ተሳትፈዋል፡፡
በዚህም 805 ነጥብ 3 ሚሊየን ችግኞች በመትከል የተያዘውን እቅድ ማሳካት መቻሉን አውስተው÷ ይህንን ታላቅ ተግባር ለፈጸመው የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መናገር ብቻ ሳይሆን በመደመር መተግበር እንደምትችል ያሳየችበት ተግባር መሆኑን አመልክተዋል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.