የጉሙዝ ብሔረሰብ የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ “ጓንዷ” በዓል በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2018 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉሙዝ ብሔረሰብ የአዲስ ዓመት ማብሰሪያ የሆነው “ጓንዷ” በዓል በአዲስ አበባ ከተማ እየተከበረ ነው፡፡
የዘንድሮው የጓንዷ በዓል “ጓንዷ ለዘላቂ ሠላምና ለሁለንተናዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተከበረ የሚገኘው።
በአከባበር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የብሔረሰቡ ተወላጆች እና የተለያዩ ብሔሮች ብሔረሰቦች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በአብሮነት ታድመዋል፡፡